1
ሚያዝያ 30 ፣ 2010 ዓ.ም.
ለክቡር ዶ/ር ዓብይ አሕመድ
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ
ጠቅላይ ሚንስቴር
ጉዳዩ፡ ክቡርነትዎ ያቀረቡትን የሰላምና ዕርቅ ራዕይ እንዲተገብሩ ስለማበረታታት እና ራዕዩን ለመተግበር
የወደፊት ትብብርና ድጋፍ ስለ ማቅረብ
ሀገራችን ኢትዮጵያ ከቅርብ አመታት ወዲህ በአሳሳቢ የፖለቲካና ማህበራዊ ቀዉስ ዉሰጥ
በመግባትዋ ሁላችንም ስጋት ገብቶን እንደ ነበር ግልጽ ነዉ። ሆኖም ክቡርነትዎ ሀገር ለማዳንና
ህዝባችንን ካንዣበበበት ሁለንተናዊ አደጋ ለመታደግ ብሎም ሰላም፣ ፍትህ፣ ዴሞክራሲና ብልጽግና
የሰፈነባትን ፤ ሁላችንም እንደ ዜጎች ተከባብረንና ተቻችለን ሰብዓዊ መብታችን ተከብሮ የምንኖርባትን
ኢትዮጵያ ለመገንባት በድፍረትና በግልጽነት እርሶ በጀመሩት እንቅስቃሴ ሀገራችን ከመቼዉም በበለጠ
የተስፋ ጮራ ፈንጥቆባታል ብለን በጽኑ እናምናልን።
በየትኛዉም አመክንዮ ፡ ሀሳብ ንግግርን፣ ንግግርም ተግባርን ስለሚቀድም ክቡርነትዎ እንደ ሀገር
መሪ ያደረጓቸዉን ንግግሮች በትልቅ አክብሮትና አድናቆት የምንቀበል መሆናችንን እየገለጽን፤ እኛ በዚህ
ደብዳቤ ግርጌ ስማችንን የዘረዘርን በዉጭ ሀገር የሚንኖር በሰላም፣ በዕርቅ፣ በመግባባትና በሰብዓዊ
መብቶች ዙሪያ ስንሰራ የቆየን ግለሰቦች የክቡርነትዎን ራዕይ በተቻለን ሁሉ ለማገዝ፤ እንዲሁም በአግባቡ
እንዲተገበሩ ለማበረታታትና ለመደገፍ የምንፈልግ መሆናችንን በታላቅ ደስታ ልናሳዉቆት እንወዳለን።
ከዚህ አንጻር እርስዎ በፓርላማ ባደረጉት ታሪካዊ ንግግር ዉስጥ ካነሷቸዉና እንዲሁም
ከዓላማችንና ከዚህ ደብዳቤ ርዕስ ጋር ተጓደኝነት ያለቸዉ ሀሰቦች ከብዙ በጥቂቱ ለማስታወስ ያህል፦
ስለ ዕርቅ፦ «መጪው ጊዜ በኢትዮጵያችን የፍቅርና የይቅርታ ጊዜ ነው!» «በአገር ውስጥም ሆነ
በስደት ከአገር ውጭ የምትኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በሙሉ ከልባችን ይቅር
ተባብለን፣ የትናንትናውን ምእራፍ ዘግተን፣ በብሔራዊ መግባባት ወደ ቀጣይ ብሩህ ሀገራዊ ምእራፍ
እንሻገር ዘንድ ጥሪዬን አቀርባለሁ።»
ስለ ሰላም፦ «ለሰላም መሰረቱ ፍትህ ነው። ሰላም የግጭት አለመኖር ብቻ አይደለም። ሰላም
በመግባባት ላይ የተመሰረተ ጽኑ አንድነታችን ነው፣ ሰላም- መተማመናችን ነው። ሰላም-በሁላችንም